Wednesday, 16 December 2015

ድግምት

           1. ድግምት፦

 ሲህር” (ድግምት) በዓረብኛ ቋንቋ ስውር የሆነና ምክንያቱ ያልታወቀ ነገር ማለት ነው፡፡

         ሸሪዓዊ ትርጉሙ፦

 ልብን ወይም አካልን በማሳመም ወይም በመግደል ተፅዕኖ የሚያሳድር እንዲሁም በባልና ሚስት መካከል የሚለያይ ልፍለፋና ትብተባ ሲሆን ነገር ግን ሁሉም ተፅዕኖ ሊያደርግ የሚችለው በአላህ ፍቃድ ብቻ ነው:: ድግምት ኩፍር ሲሆን ድግምተኛም በአላህ የካደ ካፊር በመሆኑ አኺራ ላይ ምንም ዕጣ ፈንታ የለውም፡፡

 አላህ እንዲህ ይላል፦

 ‹‹ሰይጣናትም በሱለይማን (ሰሎሞን) ዘመነ መንግስት የሚያነቡትን (ድግምት) ተከተሉ፡፡ ሱለይማንም አልካደም፤ (ድግምተኛ አልነበረም) ግን ሰይጣናት ሰዎችን ድግምትን የሚያስተምሩ ሲኾኑ ካዱ፡፡ ያንንም በባቢል በሁለቱ መላእክት በሃሩትና ማሩት ላይ የተወረደውን ነገር (ያስተምሩዋቸዋል)፡፡ «እኛ መፈተኛ ነንና አትካድ» እስከሚሉም ድረስ አንድንም አያስተምሩም፡፡ ከእነሱም በሰውየውና በሚስቱ መካከል በርሱ የሚለዩበትን ነገር ይማራሉ፡፡ እነርሱም በአላህ ፈቃድ ካልኾነ በርሱ አንድንም ጎጂዎች አይደሉም፡፡ የሚጎዳቸውንና የማይጠቅማቸውንም ይማራሉ፡፡ የገዛውም ሰው ለርሱ በመጨረሻይቱ አገር ምንም እድል የሌለው መኾኑን በእርግጥ ዐወቁ፡፡ ነፍሶቻቸውንም በርሱ የሸጡበት ዋጋ ከፋ! የሚያውቁ በኾኑ ኖሮ (ባልሠሩት ነበር)፡፡››

(አል በቀራህ 12)

 በተቋጠሩ ክሮች ላይም መትፋት አንዱ የድግምት ክፍል ነው::  አላህ እንዲህ ይላል፦

 በል «በተፈልቃቂው ጎህ ጌታ እጠበቃለሁ፡፡ ከፈጠረው ፍጡር ሁሉ ክፋት፡፡ ከሌሊትም ክፋት ባጨለመ ጊዜ፤በተቋጠሩ (ክሮች) ላይ ተፊዎች ከኾኑት (ደጋሚ) ሴቶችም ክፋት፡፡ከምቀኛም ክፋት በተመቀኘ ጊዜ፤ (እጠበቃለሁ በል)፡፡»

(አል ፈለቅ 1-5)


 ከተንኮለኛና ምቀኞች ሁሉ አላህ ይጠብቀን!!!

No comments:

Post a Comment